በሰንበት ትምህርት ቤት ከፍል የህጻናት እና ወጣቶች ትምህርት ከ level 1 እስከ level 4 በመከፋፈል የቤተክርስቲያናችንን የሃይማኖት ትምህርት በእንግሊዘኛ ቋንቋ በበጎ አድራጊ መምህራን በየሳምንቱ እሁድ ጧት (ቅዳሴ ሰዓት ስርዓተ ቁርባን እንዳላቀ) በመሰጠት ላይ ይገኛል
የአብነት ትምህረት በቤተክርስቲያናችን የአብነት መምህር መርጌታ ዮሐንስ ዘወትር ቅዳሜ ከ 10 AM – 12 PM በ zoom ይሰጣል። እንዲሁም የልጆች አማርኛ ትምህርት የመጀመሪያ ዙር በሶስት ደራጃ የሚሰጥ ይሆናል። የትምህርት ቀኑም ቅዳሜ ከ 2፡00 PM እስከ 4:30 PM ነው።
የበጎ አድራጎት ፈቃደኝነት /volunteering opportunity የወላጆች የበጎ አድራጎት ፈቃደኝነት እና የልጆች አማርኛ ትምህርት መሙያ ቅፅ የወላጆች የበጎ አድራጎት ፈቃደኝነት አገልግሎት የሚሰጠዉ በሳምንት አንድ ቀን ቅዳሜ ወይም እሁድ ከ ሁለት እስከ ሶስት ሰዓት ይሆናል። የወላጅ በጎ አገልጋዬች ዋና ተግባር የልጆች ትምህርት ያለምንም እንከን እንዲሰጥ ከአስተማሪዎች ጋር በመነጋገር ማስተባበር ይሆናል (ማስተማርን አያካትትም)። ለሚያደርጉት የተቀደሰ ተግባር በቅድሚያ እግዚአብሔር ይስጥልን። ቅጹን ለመሙላት ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ።